Monthly Archives: February 2016

ከ 207 አስገራሚና አስቂኝ የታክሲ ላይ ጥቅሶች…

ዝዋይ ቃሊቲ ቂሊንጦ's photo.
By ዝዋይ ቃሊቲ ቂሊንጦ

ከ207  አስገራሚና አስቂኝ የታክሲ ላይ ጥቅሶች…
1. እንኑር ብለን ነው እንጂ መሞት አያቅተንም!
2. የያዝናት እድሜ አይደለም ለጠብ ለፍቅር እንኩአን
አትበቃም!
3. ብቸኝነት ደስ የሚለው ሽንት ቤት ብቻ ነዉ
4. ማች ከመሞቱ በፊት ፍቅረኛውን ዜብራላይ ይስም ነበር
5. ጭቅጭቁን ትተን ብንፋቀር ምነው ሁሉም ቅርብ ወራጅ ነው
ከፈጣሪ በቀር
6. ታክሲ ዉስጥ መጨቃጨቅ ኣሸባሪነት ነው
7. ሰዉ ብቻ ነዉ የምንጭነዉ በስህትት የተሰቀለ ካለ ይዉረድ
8. የሰራ የእጁን የተቀመጠ የቂጡን ያገኛል
9. አንገትክ ብቆረጥም ዋናዉ ጤና ነዉ
10. መብትዎን ታክሲ ላይ ትዝ ኣይበልዎ
11. ጤፍና በርበሬ ሲወደድ ችላቹ ታክሲ ላይ ታማርራላቹ
12. መንግስትና ተሳፋሪ ሊወርዱ ሲሉ ነገር ነገር ይላቸዋል
13. ስልጣን የህዝብ ማስተዳደሪያ እንጂ ማስፈራሪያ አይደለም
14. የምተኛዉ የማይተኛ ጌታ ስላለኝ ነዉ
15. አምላኬ 100000000 ዶላር እና ጤንነቴን ስጠኝ
16. ጡትና መንግስት ጊዜውን ጠብቆ መውደቁ አይቀርም
17. ምከረው ምከረው አንቢ ካለ በሴት አስመክረው
18. ጎንበሥ ቀና ብዬ ባገለግላቸው ከወንዝ የተገኘ ድንጋይ
መሠልኳቸው
19. ፍቅረኛዬን አጣው ብለህ አትጨነቅ ታክሲም ማጣት አለና
20. ጠጋ ጠጋ በሉ! ! በኛ ታክሲ ተዋውቀው ብዙ ሰው ተጋብቷል
21. ነገረኛ ተሳፋሪ አደባባይ ላይ ” ወራጅ አለ ” ይላል
22. ሰውን ስትወድ ከመልካም ስብዕናው ውጪ ምኑንም ሳታይ
ይሁን
23. አንድ ማፍቀር ግድ ነው ሁለት ማፍቀር ግን ንግድ ነው
ሶስት ማፍቀር ግን ኮንትሮባንድ ነው
24. መዶሻ ጭንቅላት ያለው ሰው ሁሉም ስው ሚስማር
ይመስለዋል
25. ከሰራህ ትበላለህ ካልሰራ ሲበሉ ታያለህ
26. እግዝአብሄር ድሃን ማስደሰት ሲፈልግ አህያውን አጥፍቶ
እንዲያገኘው ያደርጋል
27. የበታችነት ከተሰማ ዛፍ ላይ ዉጣ
28. ጨበሶ ከመቃጠል በልቶ መመዘን ይሻላል
29. ቅናት ያገረጣዉ ፊት ቅባት አያወዛዉም
30. አስተዉሎ የሚራመድ ጫት ተራ ይደርሳል
31. እንኳን ተሳፋሪ ሙታንም ይሸጋሸጋል
32. ተሳፍሪ ጠጋጠጋ በሉ የአባይ አደራ አለብን
33. ባለጌ ሰው ዜብራ ላይ ወራጅ ይላል
34. ከጫት ሙቀት እንጂ አይገኝም እውቀት
35. ዜብራውን አንስተን አህያ እናስተኛልህ ወይ(ለሹፌሮች)
36. ለወሬኛ እና ለአምስት ሳንቲም መልስ የለንም
37. ፍቅር ፍቅር እያልሽ አትጨማለቂ ልቤ ዉስጥ ለመግባት
ጫማሽን አዉልቂ
38. አባይን ያላየ ሄዶ ማየት ይችላል
39. ሴት ልጅ ታርሳ የምትገኝ ቢሆን ኖሮ ወንድ ሁላ ገበሬ
ይሆን ነበር
40. ሰዉን አትናቁ ሰው እንዴት ይናቃል ቅማል እንኳን በአቅሙ
ሱሪ ያስወልቃል
41. እስቲ ይሁን ብለን የተከለዉ ቃጋ ጎበስ ጎበስ አለ እኛኑ
ሊወጋ
42. ባላገር ሲሰለጥን በዜና ይደንሳል
43. መሀይም ሀብታም ደሃን የፈጠረ ይመስለዋል
44. ምን ጊዜው ቢረዝምም ቋንጣ እና ባለ ስልጣን መውረዱ
አይቀርም
45. ዝናብ ጥሎ ጥሎ መሬቱ ጭቃ ሲሆን ያን እያነሱ
ግርግዳዉ ላይ ልጥፍ
46. በፍየል ዘመን በግ አትሁን
47. ሹፌሩን በፍቅር ማሣቅ እንጅ በነገር ማሣቀቅ ክልክል ነው
48. ትሞህርት በዱላ ቢሆን ኖሮ አህያ ፕሮፌሰር ትሆን ነበር
49. ሴት ልጅ ሒሣብ ሥትማር እንጂ ስትከፍል አይተን አናቅም
50. ደሀ ነዉ ችስታ ነዉ ብለሽ ትይኛለሽ ጭንና ዳሌ እንጂ
አንችስ ምን አለሽ
51. መልስ ለረሳ ማትሪክ ላይ እንመልሳለን
52. ሴትና ሎተሪ ለማይፈልጋቸዉ እንጂ ለሚፈልጋቸዉ
አይወጡም
53. ሹፌር ለጠበሰ ባለ 100ብር ረዳት ለጠበሰ ባለ 50
ብርካርድ እንሞላለን
54. የቅድብ ፀጉርና ምቀኛ አያድጉም
55. ንፁህ ህሊና ምቹ ትራስ ነዉ
56. ላታመልጪኝ አታሩጪኝ
57. ስራ ያጣ ተሳፋሪ ጋቢና ይቀመጣል
58. የማያልፍለት ደሃ ሀብታምን ይጋብዛል
59. በባጃጅ ስትጋዝ ንፋስ መታኝ አትበል ባጃጅ የመኪናዎች
የልጅ ልጅ ናትና
60. ደንበኛ ካልቀበጠ ንጉስ ነዉ
61. ጧት ስትሄድ በእንቅፋት የመታህ ድንጋይ ማታ ከደገመህ
ድንጋዩ አንተ እንጂ እሱ አይደለም
62. ጋይስ እንጀራ የለም እንጂ ወጥ ቢኖር ኖሮ በልታቹ ትሄዱ
ነበር
63. ድብርትንና ጥይትን ተኝቶ ማሳለፍ ነው
64. ጠጋ ጠጋ በሉ ሁሉም ቅርብ ወራጅ ነው ከፈጣሪ በቀር
65. ከድሃ ቤት ጥቅስ ከሀብታም ቤት ጥብስ አይጠፋም
66. የቤትክን አመል እዛው
67. በፍርፍር ያዘነ በጥብስ ይደሰታል በፍቅር ያዘነ…..?
68. የመኖር ወርቃማ ዘዴ መቻቻል ብቻ ነው
69. ሁለት ክንድ አንድ ሜትር ነው ከዛ ያሳለፈ ውሸታም ነው
70. የሰው ልጅ አረም የበዛበት የመከራ ተክል ነው
71. የሚፈልገውን ያላገኘ ልብ ዘውትረ መንገደኛ ነው
72. የአለም ሙቀት መጨመር መንስኤ ጭቅጭቅ ነው
73. ፈገግታዬ ብዙ ነው ልቤ ግን ለአንድ ሠው ነው
74. ባለጌና ዋንጫ ወደ አፉ ሰፊ ነው
75. መስታወት በቆጣሪ ቢሆን ኖሮ ሴቶች ምን ይዉጣቸዉ ነበር
76. ድሀ በህልሙ ቂቤ ባይጠጣ ኖሮ ምን ይዉጠዉ ነበር ?
77. ማንበብ ከቻልክበት ሁሉም ሰው መፅሀፍ ነው
78. ለሚያልፍ ቀን የማያልፍ ቃል አትናግር
79. ባጃጅን አወቅሽ አወቅሽ ሲሏት ታፔላ አወጡላት
80. ይሄ አናት ለቴስታ እንጂ ለትምህርት አይሆንም
81. ለኛ ከራሳችን የበለጠ የሚያስብልን የለም
82. ዝቅ ብለህ ስትሰራ ሁሉም ነገር ዝቅ ብሎ ይታይሃል
83. ማንም ሠው የጣለውን ሲያነሱበት አይወድም
84. ከሹፌሩ ጋር የምትጨቃጨቁ በኢቦላ እለቁ
85. ፍቅር ካለ ታክሲ ባሥ ይሆናል
86. የኪስ ሌቦች ቆዩ ሒሳቡን ሳንቀበል ስራ እንዳትጀምሩ
87. ሲጠሉህ ሳይሆን ሲወዱህም ለምን በል
88. ለሰዉ ሳይሆን ለራስህም ታመን
89. አለመዘጋጀት ለውድቀት መዘጋጀት ነው
90. ሂሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
91. ሰርቶ የማይዝናና አህያ ብቻ ነዉ
92. ሹፌሩን በፍቅር እንጂ በነገር መጥበስ ክልክል ነው
93. እንደምን አደራቹ ውሸት መሮኛል ስራ ፈልጉልኝ
94. ኑሮና ታክሲ ካልታገሱት አይሞላም
95. እስክናውቅ እንጂ እስክናብድ አንማርም
96. የትም ፍጪው ምግቡን ብቻ ስጪኝ
97. አንድን ሳትይዝ ሁለትን አታገኝም
98. ያለዉን የሰጠ ባዶዉን ይቀራል
99. ሱሪህን ሳይሆን ራስህን ዝቅ አድርገህ ኑር
100. ህይወት በደረጃ ፈተና በኩረጃ
101. ለመኖር ብላ እንጂ ለመብላት አትኑር
102. ሾርባ ያቃጠለው በርጎ ይናደዳል
103. ያልተነገረ እንጂ ያልተባለ የለም
104. ሠርቶ የማይዝናና አህያ ብቻ ነዉ
105. የጊዜ ጀግና እንጂ የሰው ጀግና የለውም
106. ሰው እና ድፎ በትዛዝ እንደፋለን
107. እንደ ባሪያ ከሰራ እንደ ንጉስ ትኖራለህ
108. አንድ ጎል እና አንድ ሚስት አትመን
109. ወይ ጉድ ሀይሩፍ በዶልፊን ይስቃል አሉ
110. ሰዉን ማመን ቀብሮ ሳይሆን ቀብድ ተቀብሎ ነዉ
111. በፍቅር ለወደቀ የመሬት ስበት ተጠያቂ አይደለም
112. የማያልፍለት ደሀ ሀብታም ይጋብዛል
113. በሰዉ ላይ ከምትስቅ መጀመሪያ ራስህን እወቅ
114. አበሻ አንድ እግሩን ካልቆጹለት የሁለተኛው እግር ጥቅም
አይገባውም
115. ከምታማ ወንጌል ሰማ
116. ዝቅ ብሎ የሠራ ከፍ ብሎ ይኖራ
117. የሰነፍ አእምሮ የሰይጣን ቤተ_ሙከራ ነዉ
118. ለስራ ያልታደለ አእምሮ ለተንኮል ማንም አይወዳደረዉም
119. የሴት ልጅ ውበቷ ታማኝኀቷ
120. ከማይረባ ጉልበት ይሸለል ልብ አርጉልኝ ማለት
121. መኖር ደጉ ብር ባያስቆጥረን ቀን ያስቆጥረናል
122. የእናት ሞትና የድንጋይ መቀመጫ እያደር ይቆሮቁራል
123. “ቀስ ብሎ ማደግን ሳይሆን ቁሞመቅረትን ፍራ”አለች
ባጃጅ!!!
124. አራዳ እናቱን ሚረዳ
125. ሞላ የሰው ስም ነዉ ተጠጉ
126. አፍ ከመክፈት ሱቅ መክፈት
127. ውፍረትና ውሸት ለባለቤቱ አይታወቅም
128. ለላዳና ለካፌ ብዙብዙ ይከፍላሉ ምነው እኛጋ ሲመጡ
ለምን ይጨቃጨቃሉ
129. አንበሳ ሲያረጅ ቢሾፍቱ መጣ
130. ያለ ምክንያት መኖር ክልክል ነዉ
131. ታክሲና መግስተ ሰማያት ሞልቶ አያውቅም
132. ሲሰሩ አትስራና አዞሩብኝ በል ስትዞር ዋልና
133. በጎ አሳቢ ከስድብ ምክር ያወጣል
134. ዝምታዬ ካልገባችሁ ንግግሬ አይገባችሁም
135. ተጠጉ ሲባሉ ቦታ የለም አይበሉ፣ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ
ነዉ
136. ጥይትንና ድህነትን ተኝቶ ነዉ ማለፍ
137. ጠጋ ጠጋ በሉ የቻይና እዳ አለብን
138. መቆጨት የለብክ በማፍቀርክ ሳይሆን ማፍቀር ያለብክን
ሠው ባለማወቅክ ነው
139. ጠንካራ ሠው በጨለማ በስተጀርባ ብርሀን ይታየዋል
140. ሣያሥቡ መናገር ሣያልሙ መተኮስ ነው
141. ጓደኞችህ አካውንት ይከፍታሉአንተ አፍህን ትከፍት አለህ
142. ከምታማኝ ምከረኝ
143. በፍየል ዘመን በግ አትሁን
144. ድንች ቢውፍር ሹካ ያነሳዋል
145. ያሳደግናት ውርንጫ መልሳ በእርግጫ
146. አመል ከሌለሽ ወደ ባስሽ።
147. ወረድ ወረድ ይህ ታክሲ እንጂ ፌስቡክ አይደለም
148. እዉነት የሚያዳምጥ እዉነት ከሚናገር አይተናነስም
149. መማሩንስ ተምረሃል ማስተዋልን ዘንግተሃል
150. ያለፈለት ሀብታም ደሀን አይጋብዝም
151. ፍቅር ማለት የምትወዳትን ልጂ ደስታ ማገኘት ማለት ነዉ
152. መኖርህ ማንንም ካልጠቀመ መሞትህ ማንንም
አይጎዳም
153. ወረኛ ገንፎ አድሮም ላቃጥል ይላል
154. ማቀድ ካልቻክ ዉድቀትህን እያቀድክነዉ
155. ያህያ ውርንጫ ጠጉሮ ጉፍፍ ያለው
156. የምንወደውን ስንከተል የምወደንን እናጣለን
157. ማስቲካ የሚታደል መስሎቹ አፋቹን አትክፈቱ
158. ይህችም እንጀራ ሆና ምጥምጣ በዝብት
159. ትችትና ሻወር ከራስ ይጀምራል
160. አራዳ እና ጭስ መውጫ አያጣም
161. ፋራ ከሚስመኝ አራዳ ይንከሰኝ
162. የምግብ ቅመሙ ረሀብ ነዉ
163. ፍቅር ካለ ፍሪጅ ይሞቃል
164. ባጎረስኩ ተነከስኩ
165. ወሬ ዳቦ አይሆንም
166. ዘሎ የወረደ ዋጋው ይቀንሳል
167. ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች አትግቡ ጋቢና ሹፈሩ ላደጋ
ይጋለጣልና
168. ብድር መጠየቅና እንግሊዝኛ መናገር ድፍረት ይጠይቃል
169. ለኔ ብላ ለኔ ብላ ትገዛለች ሊፋን መኪና
170. የምትወደዉን እስክትሰራ የምትሰራዉን ዉደደዉ
171. ፍቅር ካለ የቁንጫ ቆዳ ለሺ ሠው ይበቃል
172. በሬ ያረደና ቆንጆ ያገባ ብቻውን አይበላም
173. የዉሸት እየኖርን የእዉነት እንሞታለን
174. ከሰው ጋር ስትሆን አፍህን ብቻህን ስትሆን ራስህን
ጠብቅ
175.የማታፈቅርህን ማፋቀር ኤርፕርት ሄዶ በቡር መጠበቅ
ነዉ
176. መባልን ሳይሆን መሆንን ፍራ
177. የአራዳ ልጅ መልስ አይጠይቅም
178. ነጋልሽ ደግሞ ልትጠበሽኝ
179. ከባጃጅ ላይ ሳይከፍሉ መዉረድ ከህፃን ልጅ ላይ ዳቦ
እንደመንጠቅ ይቆጠራል
180. ገንዘብ ከድህነት እንጂ ከሞት አያስጥልም
181. እባክዎን በፀባይ ይዉረዱ እምቢ ካሉ እንደ ጋዳፊ
ይወርዳሉ
182. ሦስት ቀን ለመኖር አራት ቀን አትጨነቅ
183. እባክዎን መስኮት በመክፈት ለትራፊክ አያጋልጡን
184. ከሙስና የፀዳ የስራ ዘርፍ የታክሲ ሹፌር ብቻ ነዉ
185. ለሰዉ ቅን እንጂ ቅንቅን አትሁን
186. ከስልጣን እና ከጫት ላይ መነሳት ይከብዳል
187. ምንም ብታምሪ ከሚስትነት አታልፊም
188. ሐብታም ግጦ በጣለዉ አጥንት ደሀዉ ይሰቃያል
189. የእከክ መድሀኒት ጠንክሮ ማከክ ነዉ
190. ፊትሽ ላይ የሌለዉ የካዲስኮ ቀለም ብቻ ነዉ
191· የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ
192· ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
193· ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
194· ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
195· ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
196· ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
197· ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
198· ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
199· ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር
200· ሠው ብቻ ነው የምንጭነው በስህተት የገባ ይውረድ
201· ታክሲ ለሚጠቀሙ ብቻ
202· ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን
ላይአስተያየት፣ ቅሬታ፣ ትዝብት ወይም መሻሻል
አለበት የምትሉት ነገር ካለ
አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል::
203. ለሠው ቅን ሁን እንጂ ቅንቅን አትሁን
204· ማስቲካ የሚታደል መስሎአችሁ አፋችሁን እንዳትከፍቱ
205· መስኮቱን በመክፈት ለትራፊክ ፖሊስ አያጋፍጡን!
206· ጥብቅ ማሳሰቢያ ለክቡራን ሌቦች ሒሳብ
ሰብስበን ሳንጨርስ ስራችሁን መጀመር አትችሉም!
የማይስማማ ሌባ ካለ መውረድ ይችላል፡፡
207· ታክሲና መንግስተ ሰማያት ሞልቶ አያውቅም።