በኢትዮጵያ ታሪክ የታዩት ቀደምት የፖለቲካ ድርጅቶችና አሁን በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ፓርቲዎች አቋማቸውን የሚገልጹባቸውን ጋዜጦችና መጽሔቶች ታውቋችሃላችሁ?

የፓርቲ ልሳኖችን ይወቋቸው

(አፈንዲ ሙተቂ)
——
በኢትዮጵያ ታሪክ የታዩት ቀደምት የፖለቲካ ድርጅቶችና አሁን በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ፓርቲዎች አቋማቸውን የሚገልጹባቸውን ጋዜጦችና መጽሔቶች ታውቋችሃላችሁ…? ካላወቋችኋቸው እኚሁላችሁ፡፡

—–
1. “ሰርቶ አደር” ጋዜጣ- የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ (ኢሰፓ) ልሳን
2. “መስከረም” መጽሔት- የኢሰፓ የንድፈ ሃሳብ መጽሔት
3. “ሳገም” መጽሔት – የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ህግሓኤ) ልሳን
4. “ሀዳስ ኤርትራ” ጋዜጣ- የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ህግሓኤ) ልሳን
5. “ወይን” ጋዜጣ- የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ልሳን
6. “ዲሞክራሲያ” ጋዜጣ- የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) ልሳን
7. “የሰፊው ህዝብ ድምጽ” ጋዜጣ- የመላው ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ (መኢሶን) ልሳን
8. “በከልቻ ኦሮሚያ” ጋዜጣ- የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ልሳን (በአማርኛ የሚታተም)
9. “ሰገሌ ቦሶና” መጽሔት- የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ልሳን (በኦሮምኛ የሚዘጋጅ)
10. “ኦሮሚያ” ጋዜጣ- የኦሮሞ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ልሳን
11. “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ጋዜጣ- የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ልሳን
12. “አዲስ ራዕይ” መጽሔት- የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) የንድፈ-ሃሳብ መጽሔት
13. “ማህቶት” ጋዜጣ- የብሄረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ልሳን
14. የደቡብ ድምጽ- የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ልሳን
15. “ሄጀሶት” ጋዜጣ- የሀረሪ ብሄራዊ ሊግ ልሳን
16. “ትውልድ” ጋዜጣ- የኢትዮጵያዊያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ልሳን (አሁን በህትመት ላይ መኖሩን እንጃ)
17. “አንድነት” ጋዜጣ- የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ልሳን
18. “ፍኖተ ነጻነት” ጋዜጣ- የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ልሳን
19. “ነገረ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ- የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን
——-
ከነዚህ ጋዜጦችና መጽሔቶች መካከል የአንዳንዶቹ ህትመት ቆሟል፡፡ አንዳንዶቹ ግን ዛሬም ድረስ ይታተማሉ፡፡
ቸር ያቆየን፡፡
አፈንዲ ሙተቂ
ሚያዚያ 26/2006
—-
Afendi Muteki is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia. You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.
https://www.facebook.com/afendimutekiharar